Type a search term to find related articles by LIMS subject matter experts gathered from the most trusted and dynamic collaboration tools in the laboratory informatics industry.
በስነ አምክንዮ "በቂ" እና "አስፈላጊ" የሚሉት ቃላቶች በጣም የጠራ ትጓሜና አጠቃቀም አላቸው።
መጀመሪያ ምሳሌዎችን እንይ፡
P የተባለ አረፍተ ነገር (ድንጋጌ) Q ለተባለ ድንጋጌ እውነት መሆን አስፈላጊ ነው ከተባለ በግልባጭ ሲተረጎም "P እውነት እንዲሆን የግዴታ Q እውነት መሆን አለበት ," ወይም " P ውሸት ከሆነ Q ም ውሸት ነው" እንደማለት ይቆጠራል። ለምሳሌ ማየት በQ ቢወከልና አይን በP ቢወከል፣ P ለመሆን Q አስፈላጊ ነው። Q ከሆነ (ከታየ)፣ P እውነት ነው ማለት ነው (አይን አለ)።
ይህ ጉዳይ በሂሳብ ጥናት በቀላሉ እንደዚህ ይጻፋል፡ (Q => P), ትርጉሙም P የ"Q " መዘዝ ነው ማለት ነው። ወይም በሌላ አነጋገር Q እውን ሲሆን Pን ያመላክታል ማለት ነው። ምሳሌ፡ እይታ => አይን መኖር ፤ እይታ መፈጠሩ አይን መኖርን ያመላክታል። ወይም ደግሞ አይን መኖር የእይታ መዘዝ ነው።
ምሳሌዎች፡
P የተባለ አረፍተ ነገር Q የተባለ አረፍተ ነገር እውነት እንዲሆን በቂ ፣ ነው ካልን P እውነት መሆኑ ብቻ Qን እውነት ያደርገዋል። በሌላ ጎን P ውሸት ቢሆን Q ውሸት ነው ለማለት በቂ ማስረጃ የለንም። በሌላ አነገጋገር " P ከሆነ Q" ወይም ደግሞ "P => Q," በሚል ሲያጥር፣ " የP መሆን Qን ያመላክታል" ማለት ነው። ከዚህ አንጻር Q የP መዘዝ ነው ማለት ነው።
በሂሳብ ጥናት "በቂ" እና "አስፈላጊ" የተገላቢጦሽ ግንኙነት አላቸው። ለQ፣ P አስፈላጊ ከሆነ፣ ለP፣ Q በቂ ነው ማለት ነው። ምሳሌ፡ ድመት ለመሆን እንስሳ መሆን አስፈላጊ ሲሆን፣ በአንጻሩ እንስሳ ለመሆን ድመት መሆን በቂ ነው።
P ፣ ለ Q በቂና አስፈላጊ ነው ካልን ትርጉሙ "P ከሆነ Q እንዲሁም Q ከሆነ P" ወይም ባጭሩ "P ከሆነና ከሆነ ብቻ Q" እንደማለት ነው። በሂሳብ ሲጻፍ P <=> Q ማለት ነው። P ና Q በዚህ ወቅት ምንም ልዩነት የላቸውም፣ አንድ ናቸው ማለት ይቻላል።
ምሳሌዎች: